am_obs/content/32.md

67 lines
6.2 KiB
Markdown

# 32. ኢየሱስ ርኵስ መንፈስ የያዘውን ሰውና የታመመችውን ሴት ፈወሰ
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-01.jpg)
አንድ ቀን ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ሐይቁን አቋርጠው የጌርጌሴኖን ሰዎች ወደሚኖሩበት አካባቢ ሄዱ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-02.jpg)
ወደ ሐይቁ ማዶ በደረሱ ጊዜ ርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ሮጦ ወደ ኢየሱስ መጣ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-03.jpg)
ይህ ሰው ማንም ሊቈጣጠረው የማይችል እጅግ ብርቱ ነበረ። ሰዎች እጆቹንና እግሮቹን እንኳ በሰንሰለት አስረውት ነበር፣ ነገር ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-04.jpg)
ሰውዬው በአካባቢው ባሉ መቃብሮች መካከል ይኖር ነበር። ይህ ሰው ቀኑንና ሌሊቱን ሁሉ ይጮኽ ነበር። ልብስ አይለብስም ነበር፣ ሰውነቱንም በተደጋጋሚ በድንጋይ ይቧጭር ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-05.jpg)
ሰውዬው ወደ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ፣ በፊቱ በጉልበቱ ወድቆ ሰገደለት። ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ከዚህ ሰው ውጣ!” አለው።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-06.jpg)
ርኵስ መንፈሱ ያለበት ሰው ከፍ ባለ ድምፅ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፣ ከእኔ ምን ትፈልጋለህ? እባክህን አታሠቃየኝ!" ብሎ ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ። ከዚያም ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው” አለና መለሰ። (“ሌጌዎን” በሮማ ጦር ሠራዊት ብዙ ሺህ ወታደሮችን የያዘ ክፍል ነበር።)
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-07.jpg)
ርኵሳን መናፍስቱ፣ “እባክህን ከዚህ አካባቢ አታርቀን!” ብለው ለመኑት። በአቅራቢያው ባለ ኮረብታ ላይ የእሪያ መንጋ ተሰማርቶ ነበር። ስለዚህ ርኵሳን መናፍስቱ ኢየሱስን፣ “እባክህን በዚህ ፈንታ ወደ እሪያዎቹ ስደደን!” ብለው ለመኑት። ኢየሱስ፣ “ሂዱ!” አላቸው።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-08.jpg)
ርኵሳን መናፍስቱ ከሰውዬው ወጡና ወደ እሪያዎቹ ገቡ። እሪያዎቹ ከአፋፉ ቊልቊል ሮጡና በሐይቁ ሰጠሙ። በመንጋው 2,000 ያህል እሪያዎች ነበሩ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-09.jpg)
እሪያዎቹን ይጠብቁ የነበሩት ሰዎች የሆነውን ነገር ባዩ ጊዜ ወደ ከተማ ሮጡና ኢየሱስ ያደረገውን ነገር ላገኙት ሰው ሁሉ ተናገሩ። የከተማው ሰዎች መጡና ርኵሳን መናፍስት የነበሩበትን ሰው ዐዩ። ልብሱን ለብሶ እንደ ጤናማ ሰው ሆኖ በጸጥታ ተቀምጦ ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-10.jpg)
ሰዎቹ በጣም ፈርተው ነበርና ኢየሱስን እንዲሄድ ጠየቁት። ስለዚህ ኢየሱስ ጀልባ ውስጥ ገባና ለመሄድ ተዘጋጀ። ርኵን መናፍስት የነበሩበት ሰው ከኢየሱስ ጋር ለመሄድ ልመና አቀረበ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-11.jpg)
ነገር ግን ኢየሱስ፣ “አይደለም፣ ወደ ቤትህ ሄደህ እግዚአብሔር ስላደረገልህ ነገር ሁሉና እንዴት እንደ ማረህ ለወዳጆችህና ለቤተ ሰብህ እንድትነግር እፈልጋለሁ” አለው።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-12.jpg)
ስለዚህ ሰውዬው ሄደና ኢየሱስ ስላደረገለት ነገር ለሁሉም ሰው ተናገረ። ታሪኩን የሰማ ሰው ሁሉ በአድናቆትና በአግራሞት ተሞላ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-13.jpg)
ኢየሱስ ወደ ሐይቁ ማዶ ተመለሰ። እዚያ በደረሰ ጊዜ ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ተሰበሰቡና አጨናነቁት። በሕዝቡ መካከል ለዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት ነበረች። እንዲፈውሱአት ገንዘብዋን ሁሉ ለሐኪሞች ከፍላ ነበር፣ ነገር ግን ባሰባት።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-14.jpg)
ኢየሱስ ብዙ በሽተኞችን እንደ ፈወሰ ሰምታ ነበርና፣ “የኢየሱስን ልብስ ብቻ ብዳስስ ያኔ እኔም እንደምፈወስ እርግጠኛ ነኝ!” ብላ ዐሰበች። ስለዚህ ከኢየሱስ ኋላ መጣችና ልብሱን ዳሰሰች። ልብሱን እንደ ዳሰሰች ወዲያውኑ ደምዋ ቆመ!
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-15.jpg)
ወዲያውኑ፣ ኢየሱስ ኃይል ከእርሱ እንደ ወጣ ዐወቀ። ስለዚህ ወደ ኋላ ዞረና፣ “ማን ነው የዳሰሰኝ?” ብሎ ጠየቀ። ደቀ መዛሙርቱ፣ “በዙሪያህ የተሰበሰቡና የሚያጋፉህ ብዙ ሰዎች አሉ። ‘ስለ ምን ማን ዳሰሰኝ’ ብለህ ትጠይቃለህ?” ብለው መለሱለት።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-32-16.jpg)
ሴቲቱ እየተንቀጠቀጠችና በጣም እየፈራች በኢየሱስ ፊት ተደፋች። ከዚያም ያደረገችውን፣ እንዲሁም የተፈወሰች መሆንዋን ነገረችው። ኢየሱስ፣ “እምነትሽ አድኖሻል። በሰላም ሂጂ” አላት።
_**የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከማቴዎስ 8፡28-34፤ 9፡20-22፤ ማርቆስ 5፡1-20፤ 5፡24-34፤ ሉቃስ 8፡26-39፤ 8፡42-48።**_