am_obs/content/21.md

63 lines
7.3 KiB
Markdown

# 21. እግዚአብሔር መሲሑን ተስፋ ሰጠ
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-01.jpg)
ገና ከመጀመሪያው፣ እግዚአብሔር መሲሑንለመላክ ዐቀደ። የመጀመሪያው የመሲሑ ተስፋ ወደ አዳምና ሔዋን መጣ። እግዚአብሔርየእባቡን ራስ የሚቀጠቅጥ የሔዋን ዘር እንደሚወለድ ተስፋ ሰጠ። ሔዋንን ያታለለው እባብ ሰይጣን ነበር። ተስፋው መሲሑ ሰይጣንን ፍጹም ያሸንፈዋል ማለት ነው።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-02.jpg)
በእርሱ በኩል የዓለም ሕዝብ ወገኖች በሙሉ በረከት እንደሚቀበሉ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ ሰጠው። ይህ በረከት ወደ ፊት መሲሑ ሲመጣ ይፈጸማል። እርሱ በዓለም ካሉ ከሁሉም የሕዝብ ወገኖች የሆኑ ሕዝቦች እንዲድኑ ያደርጋል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-03.jpg)
ወደ ፊት እንደ ሙሴ ያለ ሌላ ነቢይ እንደሚያስነሣ እግዚአብሔር ለሙሴ ተስፋ ሰጠው። ይህ ቆይቶ ስለሚመጣው መሲሕ የተሰጠ ሌላ ተስፋ ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-04.jpg)
ከዝርያዎቹ አንዱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ንጉሥ ሆኖ ለዘላለም እንደሚገዛ እግዚአብሔር ለንጉሥ ዳዊት ተስፋ ሰጠው። ይህም መሲሑ ከዳዊት ዝርያዎች አንዱ ይሆናል ማለት ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-05.jpg)
እግዚአብሔር ዐዲስ ቃል ኪዳን እንደሚያደርግ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል ተስፋ ሰጠ፣ ይህ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር በሲና ከእስራኤል ጋር እንዳደረገው ቃል ኪዳን ግን አይደለም። በዐዲሱ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር ሕጉን በሕዝቡ ልብ ይጽፋል፣ ሕዝቡ በግል እግዚአብሔርን ያውቁታል፣ ሕዝቡ ይሆናሉ፣ እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ይቅር ይላል። መሲሑ ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-06.jpg)
ደግሞም የእግዚአብሔር ነቢያት መሲሑ ነቢይ፣ ካህን እንዲሁም ንጉሥ ይሆናል አሉ። ነቢይ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ከዚያም የእግዚአብሔርን ቃል ለሕዝቡ የሚያውጅ ሰው ነው። እግዚአብሔር ለመላክ ተስፋ የሰጠው መሲሕ ፍጹም ነቢይ ይሆናል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-07.jpg)
እስራኤላውያን ካህናት ስለ ኃጢአታቸው በሚደርስባቸው ቅጣት ምትክ በሕዝቡ ፈንታ ለእግዚአብሔር መሥዋዕቶችን አቀረቡ። ደግሞም ካህናት ስለ ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ። መሲሑ ፍጹም መሥዋዕት አድርጎ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚያቀርብ ፍጹም ሊቀ ካህናት ይሆናል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-08.jpg)
ንጉሥ በመንግሥቱ ላይ የሚገዛና በሕዝቡ ላይ የሚፈርድ ሰው ነው። መሲሑ በቅድማያቱ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ፍጹም ንጉሥ ይሆናል። በመላው ዓለም ላይ ለዘላለም ይገዛል፣ እንዲሁም ሁልጊዜ በቅንነት ይፈርድና ትክክለኛ ውሳኔ ይሰጣል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-09.jpg)
የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ ሌሎች ብዙ ነገሮችን ተንብየዋል። ነቢዩ ሚልክያስ መሲሑ ከመምጣቱ በፊት ታላቅ ነቢይ እንደሚመጣ አስቀድሞ ተነበየ። መሲሑ ከአንዲት ድንግል እንደሚወለድ ነቢዩ ኢሳይያስ ተነበየ። ነቢዩ ሚክያስ መሲሑ በቤተ ልሔም ከተማ ይወለዳል አለ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-10.jpg)
ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ በገሊላ ይኖራል፣ ልባቸው የተሰበረ ሰዎችን ያጽናናል፣ እንዲሁም ለተማረኩት ነጻነትንና ለታሰሩት መፈታትን ያውጃል። ደግሞም ነቢዩ መሲሑ የታመሙና መስማት፣ ማየት፣ መናገር፣ ወይም መራመድ የማይችሉትን ሕዝብ እንደሚፈውስ ተነበየ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-11.jpg)
ደግሞም ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ ያለ ምክንያት እንደሚጠላና ተቃውሞ እንደሚደርስበት ተነበየ። ሌሎች ነቢያት መሲሑን የገደሉት እነዚያ በልብሶቹ ላይ ዕጣ እንደሚጣጣሉና ወዳጁ እንደሚክደው አስቀድመው ተነበዩ። ነቢዩ ዘካርያስ መሲሑን ለሚክደው ወዳጅ ሠላሳ ብር እንደሚከፍሉት ተነበየ።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-12.jpg)
ደግሞም ነቢዩ ስለ መሲሑ አሟሟት ተናገረ። ኢሳይያስ ሰዎች መሲሑን እንደሚተፉበት፣ እንደሚያፌዙበትና እንደሚመቱት ተነበየ። ምንም ስሕተት ነገር ያላደረገ ቢሆንም እንኳ ይወጉታል በታላቅ ሕመምና ሥቃይ ይሞታል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-13.jpg)
ደግሞም ነቢያት መሲሑ ኃጢአት የሌለበት ፍጹም ይሆናል አሉ። የሌሎች ሰዎችን ኃጢአት ቅጣት ለመቀበል እርሱ ሞተ። የእርሱ መቀጣት በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ሰላምን ያመጣል። በዚህ ምክንያት መሲሑን ማድቀቅ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-14.jpg)
መሲሑ እንደሚሞትና እግዚአብሔር ደግሞ ከሙታን እንደሚያስነሣው ነቢያት አስቀድመው ተነበዩ። እግዚአብሔር በመሲሑ ሞትና ትንሣኤ በኩል ኃጢአተኞችን ለማዳን ዕቅዱን ይፈጽምና ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-21-15.jpg)
እግዚአብሔር ለነቢያት ስለ መሲሑ ብዙ ነገሮችን ገለጠላቸው፣ ነገር ግን መሲሑ ከእነዚያ ነቢያት በአንዳቸውም ጊዜ አልመጣም። ከእነዚህ ትንቢቶች የመጨረሻው ከተተነበየ ከ400 ዓመታት በኋላ፣ ልክ በትክክለኛው ጊዜ፣ እግዚአብሔር መሲሑን ወደ ዓለም ይልካል።
_የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘፍጥረት 3፡15፤ 12፡1-3፤ ዘዳግም 18፡15፤ 2ኛ ሳሙኤል 7፤ ኤርምያስ 31፤ ኢሳይያስ 59፡16፤ ዳንኤል 7፤ ሚልክያስ 4፡5፤ ኢሳይያስ 7፡14፤ ሚክያስ 5፡2፤ ኢሳይያስ 9፡1-7፤ 35፡3-5፤ 61፡53፤ መዝሙር 22፡18፤ 35፡19፤ 69፡4፤ 41፡9፤ ዘካርያስ 11፡12-13፤ ኢሳይያስ 50፡6፤ መዝሙር 16፡10-11።_