35 lines
2.8 KiB
Markdown
35 lines
2.8 KiB
Markdown
# 11. ፋሲካ
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-01.jpg)
|
|
|
|
እስራኤላውያንን ካልለቀቀ የሰዎችንና የእንስሳትን ተባዕት በኵር ሁሉ እንደሚገድል እግዚአብሔር ፈርዖንን አስጠነቀቀው። ፈርዖን ይህን በሰማ ጊዜ፣ አሁንም ማመንና ለእግዚአብሔር መታዘዝ እምቢ አለ።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-02.jpg)
|
|
|
|
እግዚአብሔር በእርሱ ያመነ የማንኛውም ሰው በኵር ወንድ ልጅ ለማዳን መንገድ አዘጋጀ። እያንዳንዱ ቤተ ሰብ ፍጹም የሆነ ጠቦት መርጦ አረደ።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-03.jpg)
|
|
|
|
እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡት፣ ሥጋውንም ጠብሰው ያለ እርሾ ከተጋገረው ቂጣ ጋር በፍጥነት እንዲበሉት ነገራቸው። ደግሞ በበሉት ጊዜ ከግብፅ ለመውጣት እንዲዘጋጁ ነገራቸው።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-04.jpg)
|
|
|
|
እስራኤላውያን ልክ እግዚአብሔር እንዲያደርጉ እንዳዘዛቸው ሁሉንም ነገር አደረጉ። እኩለ ሌሊት ላይ እግዚአብሔር በመላው ግብፅ አልፎ ወንድ በኵርን ሁሉ ገደለ።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-05.jpg)
|
|
|
|
የእስራኤላውያን ቤቶች ሁሉ በሮቻቸው ደም ተቀብተው ነበር፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቹ አለፈ። በቤቶቹ ውስጥ የነበረው ሰው ሁሉ ዳነ። እስራኤላውያን በጠቦቱ ደም ምክንያት ዳኑ።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-06.jpg)
|
|
|
|
ግብፃውያን ግን በእግዚአብሔር አላመኑም፣ ትእዛዛቱንም አልፈጸሙም። ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቻቸው አላለፈም። እግዚአብሔር የግብፃውያንን በኵር ወንዶችን ሁሉ ገደለ።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-07.jpg)
|
|
|
|
በእስር ቤት ካለው በኵር እስረኛ ጀምሮ እስከ ፈርዖን በኵር ድረስ እያንዳንዱ ግብፃዊ በኵር ወንድ ሞተ። ከጥልቅ ሐዘናቸው የተነሣ በግብፅ የነበሩ ብዙ ሰዎች ያለቅሱና ይጮኹ ነበር።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-11-08.jpg)
|
|
|
|
በዚያው ሌሊት ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “እስራኤላውያንን ይዛችሁ አሁኑኑ ሂዱ!” አላቸው።
|
|
|
|
_የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 11፡1-12፡32።_ |