31 lines
2.6 KiB
Markdown
31 lines
2.6 KiB
Markdown
# 6. እግዚአብሔር ለይስሐቅ ሚስት አዘጋጀለት
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-01.jpg)
|
|
|
|
አብርሃም በጣም ባረጀ ጊዜ ይስሐቅ ዕድሜው ለአቅመ አዳም ደረሰ። ስለዚህ አብርሃም ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ዘመዶቹ ምድር ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንዲያመጣለት ላከው።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-02.jpg)
|
|
|
|
የአብርሃም ዘመዶች ወደሚኖሩበት ምድር ከረጅም ጒዞ በኋላ ደረሰ። እግዚአብሔርም የተላከውን የአብርሃምን አገልጋይ ወደ ርብቃ መራው። ርብቃ የአብርሃም ወንድም የልጅ ልጅ ነበረች።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-03.jpg)
|
|
|
|
ርብቃ ቤተ ሰቦቿን ትታ ከአገልጋዩ ጋር ወደ ይስሐቅ ቤት ለመሄድ ተስማማች። እንደ ደረሰችም ይስሐቅ አገባት።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-04.jpg)
|
|
|
|
ከረጅም ጊዜበኋላ አብርሃምሞተና እግዚአብሔርከአብርሃም ጋርየገባው የተስፋ ቃል ኪዳን ሁሉ ወደ ይስሐቅተላለፈ። እግዚአብሔርለአብርሃም ሊቈጠር የማይችል ዘር እንደሚኖረው ተስፋ ሰጥቶት ነበር። ይሁን እንጂ የይስሐቅ ሚስት ርብቃ ልጆች ልትወልድ አልቻለችም።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-05.jpg)
|
|
|
|
ይስሐቅ ለርብቃ ጸለየላትና እግዚአብሔር መንታ ልጆችን እንድታረግዝ ፍቃዱ ሆነ። ሁለቱ ልጆች በርብቃ ማኅፀን ሳሉ እርስ በርሳቸው ይታገሉ ነበር። ርብቃም በማኅፀንዋ እየሆነ ያለው ምን እንደሆነ እግዚአብሔርን ጠየቀች።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-06.jpg)
|
|
|
|
እግዚአብሔርም ርብቃን አላት፣ “በማኅፀንሽ ካሉት ከሁለቱ ልጆች ሁለት ሕዝቦች ይወጣሉ እነርሱም እርስ በርሳቸው ይታገላሉ ታላቁም ታናሹን ያገለግላል” አላት።
|
|
|
|
![OBS Image](https://cdn.door43.org/obs/jpg/360px/obs-en-06-07.jpg)
|
|
|
|
የርብቃ ልጆች በተወለዱ ጊዜ ታላቁ ልጅ ቀይና ፀጉራም ሆኖ ወጣ ‘ኤሳው’ ሲሉትም ስም አወጡለት፤ ታናሹም ልጅ የኤሳውን ተረከዝ ይዞ ወጣ ስሙንም ‘ያዕቆብ’ ሲሉ አወጡለት።
|
|
|
|
_የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘፍጥረት 24፡1-25፤ 26።_ |